News

የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ትምህረት ጽ/ቤት የተለያዩ መፅሐፍትን እና ቦርሳዎችን የወረዳው ስራ አመራር ኃላፊዎች በተገኙበትና ቦርሳዎቹን እንዲወስዱ የተመረጡ ተማሪዎች ባሉበት የካቲት 17 ቀን 2008 ዓ.ም አስረከበ፡፡

የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ትምህረት ጽ/ቤት የተለያዩ መፅሐፍትን እና ቦርሳዎችን የወረዳው ስራ አመራር ኃላፊዎች በተገኙበትና ቦርሳዎቹን እንዲወስዱ የተመረጡ ተማሪዎች ባሉበት የካቲት 17 ቀን 2008 ዓ.ም አስረከበ፡
በርክክቡ ስነሥርዓት የዋና ኦዲተር መ/ቤት የውጭና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አወቀ ጤናው መፅሐፍቱንና ቦርሳዎቹን ባስረከቡበት ወቅት መ/ቤቱ በአዋጅ ከተሠጠው ሥልጣንና ሓላፊነት በተጨማሪ መህበራዊ ግዴታውን መወጣት እንደሚያስፈልግ በመግለፅ በተቋሙ ቤተ መፀሐፍት ተመሳሳይ ኮፒ ከሆኑት ውሰጥ 287 መፅሐፍትን እንዲሁም 169 ቦርሳዎቸን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ትምህረት ጽ/ቤት በስጦታ ለመስጠት እንደወሰነ አስረድተዋል፡፡
የወረዳው ፋይናንስና ኢኮኖሚክስ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሁሴን ጀማል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ለወረዳው መፅሐፍቱንና ቦርሳዎቹን በስጦታ ማበርከቱን አመስግነው ተቋሙ መህበራዊ ግዴታውን ለመወጣት እያደረገ ያለውን ድጋፍ በማድነቅ በቀጣይም መሰል ድጋፎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ተናግረዋል፡፡
ዋና ኦዲተር መ/ቤት ያደረገልን ስጦታ ጠቀሜታው ከፍተኛ መሆኑን የገለፁት በወረዳው የሥርዓተ ፆታና ባለዘርፈ ብዙ ባለሙያ አቶ ሻንበል አበራ በዕለቱ ከጥቁር አንበሳ ት/ቤት ለመጡ መስማት የተሳናቸው ተማሪዎች ቦርሳዎቹን አድለዋል፡፡ መፅሐፍቱም በወረዳው ለሚገኙ የተለያዩ የህዝብ ቤተመፅሐፍት እንደሚተላለፍ ገልፀዋል፡፡
በዕለቱ የተገኙ ተማሪዎችም ስማቸው እየተጠራ ቦርሳዎቹ የተሰጣቸው ሲሆን ተማሪዎቹም በተደረገላቸው ድጋፍ ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡
xx xy

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *