News

መ/ቤቱ ለጋምቤላ ክልል ዋና ኦዲተር መ/ቤት የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ

የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ለጋምቤላ ክልል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ኦዲተሮች በክዋኔና በነጠላ ኦዲት አሰራሮች ላይ ያተኮረ የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ፡፡

ከታህሳስ 22-28 ቀን 2017 ዓ.ም ለ 5 ተከታታይ ቀናት በጋምቤላ ከተማ በተሰጠው ስልጠና የክዋኔና የነጠላ ኦዲት ምንነት፣ ጠቀሜታ እንዲሁም አሠራር የተመለከተ መሆኑን የመ/ቤቱ የትምህርትና ሥልጠና ዳይሬክቶሬት  መረጃ ያመለክታል፡፡

ስልጠናውን የተከታተሉት የክልሉ ዋና ኦዲተር መ/ቤት ሰልጣኞች በሰጡት አስተያየት የክዋኔ ኦዲት ለመጀመር የሚያስችልና የነጠላ ኦዲትን ከመደበኛው ኦዲት ጋር አጣጥሞ ለማከናወን የሚረዳ ስልጠና መሆኑንና ይህም ለስራቸው ጠቃሚ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በስልጠናው 40 የሚሆኑ የክልሉ ዋና ኦዲተር መ/ቤት የኦዲት የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *