Uncategorized

መ/ቤቱ ለአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት የላፕቶፕ ኮምፒውተር ድጋፍ አደረገ

የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ለአፋር ብሔራዊ  ክልላዊ መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት መገልገያ የሚሆኑ የ15 ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች ድጋፍ አደረገ፡፡

መጋቢት 16 ቀን 2014 ዓ.ም በመ/ቤቱ በተከናወነው የርክክብ ስነስርዓት ላይ ኮምፒውተሮቹን ያስረከቡት የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት የፋይናንስ ፣ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ አሳዬ ሲሆኑ ወ/ሮ አሚና አደን የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት የንብረት ክፍል ኃላፊ ድጋፉን ተረክበዋል፡፡

መ/ቤቱ ቀደም ባሉት ጊዜያት ለተለያዩ የክልል ዋና ኦዲተር ቢሮዎችና  ሌሎች መንግስታዊ ተቋማት ተመሳሳይ የላፕቶፕ ኮምፒውተሮች እና  የቢሮ መገልገያዎችን ድጋፍ አድርጓል፡፡

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *