News

መ/ቤቱ ለሶማሌ ክልላዊ መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት ኦዲተሮች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ

የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ለሶማሌ ክልላዊ መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት ኦዲተሮች የፋይናሺልና ክዋኔ ኦዲት ሂደትና አተገባበርን በሚመለከት የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ፡፡

ከህዳር 21 -25 ቀን 2017 ዓ.ም ለ 5 ተከታታይ ቀናት በሶማሌ ክልላዊ መንግስት ጅግጅጋ ከተማ  በተሰጠው ስልጠና 68 የሚሆኑ የክልሉ ዋና ኦዲተር መ/ቤት የኦዲት የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል፡፡

ስልጠናው በተለያዩ የኦዲት አርዕስቶች ላይ የኦዲት ሂደቶችንና የትግበራ ደረጃዎችን ትኩረት አድርጎ የተሰጠ መሆኑን ከመ/ቤቱ ትምህርትና ስልጣን ዳይሬክቶሬት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት የክልል ዋና ኦዲተር መ/ቤቶችን አቅም የማጎልበት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *