Uncategorized

ለመ/ቤቱ ሠራተኞች የአስተዳደርና የህግ ማዕቀፎች ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ

የፌዴራል ዋና ኦዲተር በምስራቅ ወኪል መ/ቤት ሥር ለሚሠሩ 16 ሠራተኞች በመ/ቤቱ የአስተዳደርና የህግ ማዕቀፎች ላይ መሰረት ያደረገ ስልጠና ተሰጠ፡፡

ከጥቅምት – እስከ ጥቅምት -/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ በሚገኘው የምስራቅ ወኪል መ/ቤት በመ/ቤቱ የህግ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት አማካይነት በተሰጠው የሁለት ቀናት ስልጠና የፌዴራል መንግስት ሰራተኞች አዋጅ፣ የዋና ኦዲተር መ/ቤት የሰራተኞች አስተዳደር ደንብ እንዲሁም የዲሲፕሊን አፈፃፀምና የቅሬታ አቀራረብ ስነ-ስርዓት ደንብ ላይ ያተኮረ መሆኑ ታውቋል፡፡

የስልጠናው ዓላማም በዋናነት የመ/ቤቱ አባላት ሥራቸውን ሲያከናውኑ መብትና ግዴታቸውን አውቀው በተቀመጡ የህግ አግባቦች መሠረት ስራቸውን እንዲያከናውኑ ለማስቻል ነው ተብሏል፡፡

ቀደም ባሉት ቀናት ተመሳሳይ ስልጠናዎች ለሌሎች የመ/ቤቱ ወኪል መ/ቤቶች መሰጠቱ ይታወቃል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *