News

መ/ቤቱ ለሀረሪ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት ኦዲተሮች ስልጠና ሰጠ

የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ለሀረሪ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት የኦዲት የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በተለያዩ ኦዲት ነክ እና የአሠራር ስርዓቶች ዙሪያ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጠ፡፡

ጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም ተጀምሮ አስከ ጥቅምት 11 ቀን 2016 ዓ.ም የቆየውና በሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ በተሰጠው ስልጠና 63 የሚሆኑ የክልሉ ዋና ኦዲተር መ/ቤት የኦዲት የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡

ስልጠናው በፋይናንሽያል ኦዲት ማንዋል ላይ ያተኮረ መሆኑን ከመ/ቤቱ የትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት የተለያዩ የክልል መንግስታት ዋና ኦዲተር መ/ቤቶች አመራሮችንና ባለሙያዎችን አቅም አስፈላጊ በሆኑ ስልጠናዎች እየገነባ መሆኑ ይታወቃል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *