News

ለመ/ቤቱ የማኔጅመንት አባላት የአመራርነት አቅም ማጎልበቻ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ

ለፊዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት የአመራር አካላት በአስተሳሰብ/አመለካከት ግንባታ (Mind set) በአመራርነት ክህሎት (Leader ship) ፣ በስሜት ብልህነት( Emotional Intelligence) እና በሌሎች ተዛማጅ የአመራርነትና የአእምሮ ማበልጸጊያ ይዘቶች ዙሪያ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ፡፡

የፌዴራል ዋና ኦዲተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት ዳምጤ የስልጠናውን መርሀ ግብር ሲከፍቱ ባደረጉት አጭር ንግግር ስልጠናው የመ/ቤቱን አመራሮች የአመራርነት እና የአስተሳሰብ  ክህሎት የበለጠ ለማጎልበት የተዘጋጀ በመሆኑ በርካታ ዕውቀትና ክህሎት የሚገኝበት እንደሚሆን እምነታቸውን ገልጸው ወደፊት በሚዘጋጁ መርሀ ግብሮች ለሌሎች የመ/ቤቱ ሠራተኞችም ተመሳሳይ የአእምሮ የአቅም  ማጎልበቻ ስልጠናዎች ይሰጣሉ ብለዋል፡፡

ከታህሳስ 14-19 /2015 ዓ.ም በሚቆየው ስልጠና የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ በየደረጃው ያሉ አመራር አካላት የሚሳተፉ ሲሆን የስልጠናው ትኩረት የመሪዎች ራዕይ (Vision for Leaders)፣ ራስን መቆጣጠር( Self-Management)፣ የአነጋገር ክህሎት( Speaking skill) ፣የመሪዎች ባህሪያት (Leaders Traits) እና የስጋት ስራ አመራር( Risk Management) በሚሉና በሌሎች ተያያዥ ይዘቶች ዙሪያ እንደሚሆን ታውቋል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *