News

የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት የስራ ጉብኝት አደረጉ

በኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ  ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የተመራና ም/ኮሚሽነር ጀነራሎችን ጨምሮ የተለያዩ የሥራ ኃላፊዎች የተካተቱበት የፌዴራል ፖሊስ የአመራር ቡድን መጋቢት 11 ቀን 2017 ዓ.ም በፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት በመገኘት የስራ ጉብኝት አድርጓል፡፡

የኮሚሽኑ አመራሮች በሁለቱ መ/ቤቶች የጋራ የትብብር ሥራዎችን በተመለከተ ከፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት የበላይ አመራሮች ጋር የሁለቱን ተቋማት የጋራ ጉዳዮች በሚመለከት  ውይይት ያደረጉ ሲሆን ከውይይታቸው በኋላም የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤትን አሠራርና በአዲስ መልክ ታድሶ በስራ ላይ የዋለውን የመ/ቤቱን ህንጻና የስራ ቢሮዎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *