በፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ለውስጥ ኦዲት ዳይሬክቶሬት ኦዲተሮች የፋይናንሻል ኦዲት የአሰራር ማኑዋልን በሚመለከት የሶስት ቀን ስልጠና ተሰጠ፡፡
ከጥር 23 ቀን 2014 ዓ.ም እስከ ጥር 25 ቀን 2014 ዓ.ም በመ/ቤቱ የስልጠና አዳራሽ የተካሄደውን ስልጠና የሰጡት የመ/ቤቱ የውስጥ ኦዲት ዳይሬክተር አቶ ጥላሁን ከበደ ሲሆኑ የውስጥ ኦዲት ምንነትንና አተገባበሩን የሚመለከቱ ዝርዝር ርዕሰ ጉዳዮች በስልጠናው ተዳሰዋል፡፡