News

በተለያዩ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክህሎቶች ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተጀመረ

የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ሁሉንም አመራርና ሠራተኞች የሚያካትትና በተለያዩ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክህሎቶች ላይ ያተኮረ የአንድ ወር የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና ስርዓቶች ግንዛቤ ማስጨበጫ ወር በሚል በመ/ቤቱ የኢንፎርሜሽን ሲስተም ሰርቪስ ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀው ስልጠና 19 በሚሆኑ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ  የስልጠና ርዕሶች ላይ አተኩሮ  ከግንቦት 1 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ወር ያህል እንደሚሰጥ ታውቋል፡፡

ስልጠናው በመ/ቤቱ የስልጠና ክፍሎች በገጽ-ለገጽ ወይም በመስክ ሥራ ላይ ለሚገኙ ሠራተኞች ደግሞ በአማራጭ በኦንላይን ሥርዓት በማይክሮሶፍት ቲምስ (Microsoft Teams) አማካይነት የሚሰጥ መሆኑም ተገልጿል፡፡

ሰልጣኞች በተለያዩ ምድቦች በመሆን በተመረጡላቸው ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ በጽንሰ-ሀሳብ እና በተግባር የተደገፈ ስልጠና እንደሚከታተሉም ተመልክቷል፡፡

ስልጠናው ከመሰረታዊ የኮምፒውተር ዕውቀትና ክህሎት ጀምሮ ሰፊና ጥልቀት ያላቸው የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ርዕሰ ጉዳዮችን  የሚዳስስና በቀጥታ በመ/ቤቱ ሠራተኞች ስራ ላይ አጋዥ እንዲሆን ታስቦ የተዘጋጀ በመሆኑ ጠቀሜታው እንደ ግለሰብም ሆነ እንደ ተቋም የጎላ መሆኑን ከመ/ቤቱ የኢንፎርሜሽን ሲስተም ሰርቪስ ዳይሬክቶሬት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *