News

በስርአተ ፆታ እና በስርዓተ ፆታ ማከተት ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ

በፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የሴቶች፣ ወጣቶችና ህጻናት ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀና የስርአተ ፆታ እና የስርዓተ ፆታ ማከተትን ጽንሰ ሀሳብ መሰረት ያደረገ ስልጠና ለመ/ቤቱ የማኔጅመንት አባላት ተሰጠ፡፡

ግንቦት 24 ቀን 2014 ዓ.ም ለግማሽ ቀን በተሰጠው ስልጠና ላይ የመ/ቤቱ የማኔጅመንት አባላት የተሳተፉ ሲሆን ስልጠናውን የመ/ቤቱ የሴቶች፣ ወጣቶችና ህጻናት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ጽጌ ጥላሁን ሰጥተዋል፡፡

ስልጠናው የስርዓተ ጾታ ምንነት፣ የስርዓተ ጾታ ማካተት ጽንሰ ሀሳብ፣ ትርጉምና አተገባበርን የተመለከቱ ዝርዝር ሀሳቦች የቀረቡበት መሆኑ ታውቋል፡፡

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *