News

ለድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መ/ቤት ኦዲተሮች ስልጠና ተሰጠ

የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ለድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መ/ቤት ኦዲተሮች በተለያዩ የኦዲት አሠራሮች ዙሪያ ስልጠና ሰጠ፡፡

ከጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም  አስከ ጥቅምት 16 ቀን 2016 ዓ.ም በቆየው ስልጠና 40 የሚሆኑ የአስተዳደሩ ዋና ኦዲተር መ/ቤት የኦዲት የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡

ስልጠናው በዋናነት በአዲሱ የፋይናንሽያል ኦዲት ማንዋል ላይ ያተኮረ ሲሆን ሰልጣኞች በስልጠናው ወቅት ያደረጉት ተሳትፎም አበረታች መሆኑን ከመ/ቤቱ የትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተገኘው መረጃ ይጠቁማል፡፡

መ/ቤቱ ለእራሱ ኦዲተሮች እያደረገ ካለው ተከታታይ የአቅም ግንባታ ስራ በተጓዳኝ የተለያዩ የክልል መንግስታትና የከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መ/ቤቶች አመራሮችንና ባለሙያዎችን አቅም ለማሳደግ በርካታ ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *